Ethiopia

[email protected]
HOME NEWS PRESS CULTURE EDITORIAL ARCHIVES CONTACT US
HOME
NEWS
PRESS
CULTURE
RELIGION
ARCHIVES
MISSION
CONTACT US

LINKS
TISJD Solidarity
Abbay Media
Ethiopian News
Dagmawi
Justice in Ethiopia
Ethio Quest
MBendi
AfricaNet.com
Index on Africa
World Africa Net
Africalog

 

INT'L NEWS SITES
Africa Confidential
African Intelligence
BBC
BBC Africa
CNN
Reuters
Guardian
The Economist
The Independent
The Times
IRIN
Addis Tribune
All Africa
Walta
Focus on Africa
UNHCR

 

OPPOSITION RADIO
Radio Solidarity
German Radio
Voice of America
Nesanet
Radio UNMEE
ETV
Negat
Finote Radio
Medhin
Voice of Ethiopia

 

 


Reporter: በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳሳቢነት ጥሩነሽ ዲባባ እና ጌጤ ዋሚ መሬት እንዲመልሱ ታዘዙ

Sunday, 19 July 2009

በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር አሳሳቢነት
ጥሩነሽ ዲባባ እና ጌጤ ዋሚ መሬት እንዲመልሱ ታዘዙ
በአሰግድ ተፈራ

ከሳዑዲ አረቢያ ኤምባሲ ተወስዶ ለአትሌት ጌጤ ዋሚና ለአትሌት ጥሩነሽ ዲባባ የተሰጠውን መሬት የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ተመልሶ ለኤምባሲው እንዲሰጥ የሰጠው ትዕዛዝ ተፈፃሚ እንዲሆን የአዲስ አበባ አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ አሳሰቡ፡፡

 

ሥራ አስኪያጁ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር የፃፈውን ደብዳቤ በመጥቀስ ለመሬትና ይዞታ አስተዳደር የፃፉት ደብዳቤ እንደሚያስረዳው ሁለቱ አትሌቶች ከአራት ዓመት በፊት የሊዝ ኪራይ ዋጋ ከፍለው የወሰዱት መሬት ለሳዑዲ ኤምባሲ እንዲመለስ የተሰጠው የጊዜ ገደብ ሁለት ሳምንት ብቻ ነው፡፡

ቀደም ሲል የሳዑዲ ኤምባሲ ቦሌ ዓለም ሕንፃ ፊት ለፊት ይዞት የነበረውን ቦታ ለኤምባሲው ደህንነት አመቺ ባለመሆኑ አስተዳደሩ መሬቱን ለሌላ ወገን ቢሰጠው እንደሚስማማ ገልፆ ደብዳቤ ፅፎ ነበር፡፡ ከአስተዳደሩ የተገኘው መረጃ እንደሚያመለክተው መሬቱ በድጋሚ ለኤምባሲው እንዲሰጥ የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር በደብዳቤ ጥያቄ ያቀረበው ኤምባሲው በድጋሚ መሬቱ ይመለስልኝ ብሎ በመጠየቁ ነው፡፡

የኤምባሲውን ጥያቄ ጠቅሶ ውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ለአዲስ አበባ አስተዳደር በፃፈው ደብዳቤ "በሳዑዲና በኢትዮጵያ መካከል የቆየው ግንኙነትና ትስስር ይበልጥ እንዲጠናከር" ሲባል መሬቱ እንደገና ለኤምባሲው እንዲመለስ ይጠይቃል፡፡

የአዲስ አበባ አስተዳደር ሥራ አስኪያጅ መሬቱ ለኤምባሲው እንዲመለስ ትዕዛዝ በሰጠበት ደብዳቤ በኤምባሲው ፈቃድ መክኖ የነበረው የኤምባሲው ካርታ ተመልሶ ሥራ ላይ እንዲውል የቀድሞው ትዕዛዝ እንዲሻር፣ ለአትሌቶቹ ተመሳሳይ ቦታ እንዲዘጋጅ፣ ይህ ሁሉ ተከናውኖ በሁለት ሳምንት ጊዜ ውስጥ ሪፖርት እንዲቀርብላቸው ጠይቀዋል፡፡

የአዲስ አበባ አስተዳደር ዋና ሥራ አስኪያጅ ትዕዛዝ የደረሰው የአስተዳደሩ የመሬት ልማት አስተዳደር በተዋረድ ለቦሌ ክፍለ ከተማ ትዕዛዝ መስጠቱን ተከትሎ አትሌቶቹ የተሰማቸውን ቅሬታ ለተለያዩ የአስተዳደሩ አካላት እየገለፁ መሆናቸው ታውቋል፡፡

1997 .. አስተዳደሩ አትሌቶችን በመሰብሰብ "". እናንተ ለአገር ጥሩ ሰርታችኋል፡፡ በላባችሁ ባገኛችሁት ገንዘብ መሬት ቢሰጣችሁ በሊዝ ገዝታችሁ ከባንክ ሳትበደሩ ማልማት ትችላላችሁ" በማለት መሬት በሊዝ እንዲወስዱ መጠየቃቸውን፣ እነሱም እጣ በማውጣት በአስተዳደሩ ጥያቄ መሠረት የሊዝ ክፍያውን አጠናቀው ሃያ ሁለት ማዞሪያ ትራፊክ /ቤት የያዘው መሬት ቢሰጣቸውም የትራፊክ ጽሕፈት ቤቱ ቦታውን እፈልገዋለሁ በማለት ለዓመታት ክርክር ሲካሄድ ቆየ፡፡ አትሌቶቹ ከአራት ዓመት በኋላ በቦሌ አካባቢ ተለዋጭ ቦታ እንደተሰጣቸው ለዲዛይን፣ ለአፈር ምርመራና በዲዛይኑ መሠረት ለሕንፃ ግንባታ የሚሆን እቃ ከውጪ አገር በውጪ ምንዛሬ ማዘዛቸውን ይናገራሉ፡፡

"
ኤምባሲው ቀደም ሲል ለደህንነቴ ያሰጋኛል፡፡ ለሌሎች አልሚዎች ይሰጥ ያለውን ቦታ መልሶ ይሰጠኝ ሲል ፈቃድ መስጠት የልጆች ጨዋታ ይመስላል" በማለት ቅሬታቸውን ያቀረቡት የአትሌቶቹ ቤተሰቦች "አንድ ጊዜ ውሰድ፣ አንድ ጊዜ መልስ ማለት አሳዛኝ ነው" ብለዋል፡፡ ቦታውን ከተነጠቁት አትሌቶች መካከል "መንግሥት እንደ ዜጋ እያየን አይደለም እየተጉላላን ነው" በማለት ቅሬታዋን ገልፃለች፡፡

70
ሚሊዮን ብር የሚፈጅ ሕንፃ ለማስገንባት ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁትን አትሌት ጥሩነሽ ዲባባና ባለቤቷ አትሌት ስለሺ ስህን ስለጉዳዩ ተጠይቀው "ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የበላይ ባለሥልጣናት አቤቱታቸውን በየደረጃ እያቀረብን ነው" ብለዋል፡፡

የአዲስ አበባ አስተዳደርን በስልክ ለማነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም፡፡ የቦሌ ክፍለ ከተማ ግን "ትዕዛዝ ከተሰጠ ተግባራዊ ማድረግ ግዴታችን ነው" የሚል መልስ ሰጥቷል፡፡

በተያያዘ ዜና በተመሳሳይ መልኩ ሚሌኒየም አዳራሽ ጐን ለአትሌት ኃይሌ /ስላሴ የተሰጠው መሬት ውዝግብ ተነስቶበት ወደ ልማት ሳይገባ እንደቆየ ለማወቅ ተችሏል፡፡

Last Updated ( Sunday, 19 July 2009